22/06/2026
“ያለ ጥናትና ምርምር መሪነት የሚከናወን ሥራ፤ በጨለማ በድፍረት እንደ መጓዝ ነው” አቶ ይታሰብ ስዩም
ቱ ማ ኢ
ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም
የፌዴራል ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ተቋማዊ እድገቱን ይበልጥ ለማጠናከር ያለመና በበጀት ዓመቱ በአሰልጣኞቹና ተመራማሪዎቹ የተሰሩ አጠቃላይ የጥናትና ምርምር ሥራዎች ይፋ የተደረጉበት የምርምር መድረክ እየተካሄደ ነው።
ይህ መድረክ የተቋሙ አንጋፋ አሰልጣኞችና ተመራማሪዎች በቱሪዝም እና ሆስፒታሊቲ ዘርፍን ላይ ያሉ አሰራሮችን ለማዘመንና ውጤታማነታቸውን ለማሳደግ ታስበው የተሰሩ 6 (ስድስት) መሠረታዊና ከተግባራዊ ሥራ ጋር የተገናኙ የምርምር ሥራዎቻቸውን የሚቀርብበት ነው።
የምርምር መድረኩን በንግግር የከፈቱት የጥናትና ምርምር ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ይታሰብ ስዩም፤ በማንኛውም ተቋማዊ ዕድገት ውስጥ በማስረጃና በምክንያት ላይ የተመሰረቱ ጥናቶች ያላቸውን ምትክ የሌለው ሚና አጽንኦት ሰጥተው አብራርተዋል።
“ማንኛውንም የአሠራር ማዕቀፍ ሁለንተናዊ ከሆነ የጥናትና ምርምር መሪነት ውጭ ለመተግበር መሞከር በጨለማ ውስጥ በድፍረት እንደመጓዝ ይቆጠራል” ያሉት አቶ ይታሰብ፤ “በአሁኑ ዘመናዊ ማኅበረ-ኢኮኖሚያዊ እውነታ ውስጥ፣ ተቋማዊ ተልእኮዎችን ያለ ጥልቅና ሳይንሳዊ ምርምር ለማሳካት መሞከር በፍጹም አማራጭ ሊሆን አይችልም” ሲሉ ገልጸዋል።
ይፋ የተደረጉት ስድስቱም የምርምር ሥራዎች ሙሉ በሙሉ በተቋሙ የውስጥ አሰልጣኝ ተመራማሪዎች የተሰሩ በመሆናቸው፤ ግኝቶቹ በቀጥታ እውነታውን መሠረት ያደረጉና ተግዳሮቶችን የሚፈቱ ናቸው ተብሎ ይጠበቃል።
መርሃ ግብሩ ኢንስቲትዩቱ ጥራት ያለው ስልጠና ከመስጠት ባለፈ፤ ለዘርፉ የዕውቀት ምንጭና የምርምር ማዕከል የመሆን አቅሙ እያደገ መምጣቱን የሚያሳይ ነው ተብሏል።
በዚህ የጥናትና ምርምር መድረክ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ትክክለኛ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን ማስፈንጠሪያዎች ይጠቀሙ
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/tticommunication
ቴሌግራም ፡https://t.me/tticommunication
http://tiktok.com/
20/06/2026
በሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ የትብብር ስልጠናን ለማጠናከር የሚያስችል የምክክር መድረክ ተካሄደ::
ቱ.ማ.ኢ
ሰኔ 13/2018 ዓ ም
የፌዴራል ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት በሆቴልና በቱሪዝም ዘርፍ ለሰልጣኞች የትብብር ስልጠና (Cooperative Training) ከሚሰጡ ባለድርሻ አካላት ጋር ጠንካራ ቅንጅት ለመፍጠር የሚያስችል የምክክር መድረክ አካሄደ።
የፕሮግራሙ መክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኢንስቲትዩቱ የስልጠናና አቅም ግንባታ ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ሀብታሙ ክብረት ሲሆኑ የዘርፉን ተወዳዳሪነት ለማሳደግና ብቁ የሰው ኃይል ለማፍራት የባለድርሻ አካላት ትብብር ወሳኝ መሆኑን ገልጸዋል።
በትብብር ስልጠና ዙሪያ ሰልጣኞች ተሰማርተውባቸው ከነበሩ የሆቴልና የቱሪዝም ተቋማት የነበሩ ሂደቶችን ያጋጠሙ ችግሮችና የተወሰዱ መፍትሔዎችን ጭምር የሚዳስስ ገለጻ ያቀረቡት የትብብር ስልጠና አስተባባሪና አሰልጣኝ አቶ ሳለአምላክ ፈንታ ናቸው፡፡
እንደ አቶ ሳለ አምላክ ገለጻ ሰልጣኞችን ከመቀበል ጀምሮ በወሰዱት ኮርስ መሠረት በመመደብ እና አስፈላጊውን ክትትል በማድረግ ትክክለኛ ውጤት እስከ መሙላት ለተወጡት ኃላፊነት ምስጋናም አቅርበዋል፡፡
ይህ ስልጠና ለሰልጣኞች የተግባር ክህሎትን በተጨባጭ የስራ አካባቢ እንዲቀስሙ፣
ለአሰልጣኝ ተቋማት (ለሆቴሎችና ቱሪዝም ድርጅቶች)፡ የገበያውን ፍላጎት ያማከለ የሰው ኃይል በቅርበት እንዲያገኙ እድል የሚፈጥር በመሆኑ ለድርጅቶቹም ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑ ተገልጿል፡፡ በዚህም መሰረት በትብብር ስልጠና የነበረው የዓመቱ እቅድ አፈጻጸም 96 በመቶ መሆኑ ተገልጿል።
በመቀጠልም በቤት አያያዝ እና ላውንደሪ ሰርቪስ ስልጠና የሰልጣኝ መጥፋት እና በሆቴሎችና መስል ድርጅቶች ደግሞ ያለው ፍላጎት መጨመር ምክንያቶቹን እና የሌሎች ሀገራት ተሞክሮ እና መወሰድ ያለባቸውን መፍትሔዎች የሚጠቁም ጥናት በአቶ ሰይድ ተስፋዬ ቀርቧል።
ለውይይት በቀረቡ መነሻ የሆኑ ጹሁፎች ከተሳታፊዎች ጋር ውይይት ተደረጓል።
በማጠቃለያው የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ነጋሽ በቀጣይ ስልጠናውን ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ በጋራ መስራት አስፈላጊ መሆኑ፣ የበቃ የሰው ኃይል ለማፍራት የኢንደስትሪውና የስልጠና ተቋማት ትብብር ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት መሆኑ ከቤቱ በተነሱ ሀሳቦች መረዳት ይቻላል ብለዋል።
የስልጠናው አቀራረብ የንድፈሃሳብ 30 ፣ የተግባር 40 በተቋም አጠቃላይ 70 በመቶ ሲሆን ከኢንደስትሪው ደግሞ 30 በመቶ የሚሸፈን ነው፡፡
ትክክለኛ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን ማስፈንጠሪያዎች ይጠቀሙ
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/tticommunication
ቴሌግራም ፡https://t.me/tticommunication
http://tiktok.com/
19/06/2026
"የህፃናትን መብት መጠበቅ የወደፊቱን ትውልድ መገንባት ነው"
ቱ.ማ.ኢ
ሰኔ 12/2018 ዓ.ም
የፌዴራል ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት የአፍሪካ ህፃናት ቀንን በኢንስቲትዩቱ የህፃናት ማቆያ ካሉ ህፃናትና ቤተሰቦቻቸው ጋር አከበረ።
ከህፃናቱ ጋር በዓሉን ያከበሩት የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ነጋሽ ህፃናት የነገ ሀገር ተረካቢዎች በመሆናቸው ጥበቃና እንክብካቤ ማድረግ ግዴታ አለብን ብለዋል።
የህፃናት ማቆያው ለህፃናቱ ምቹ ለወላጆች ደግሞ ረፍት የሰጠ መሆኑን ወላጆች ተናግረዋል።
የሴቶችና ማህበራዊ አካቶ ትግበራ ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ንግስት ሲሳይ በበኩላቸው በዓሉ "የህፃናትን መብት መጠበቅ የወደፊቱን ትውልድ መገንባት ነው" በሚል መሪ ቃል ሰኔ ዘጠኝ የተከበረውን የህፃናት ቀን መልእክትና መከበር የጀመረበትን ታሪክ አካፍለዋል።
ትክክለኛ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን ማስፈንጠሪያዎች ይጠቀሙ
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/tticommunication
ቴሌግራም ፡https://t.me/tticommunication
http://tiktok.com/
15/06/2026
ኢንስቲትዩቱ የቴክኒካል አማካሪ ቦርድ አባላትን አመሰገነ
ቱ.ማ.ኢ
ሰኔ 8/2018 ዓ.ም
የቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ላለፉት ሦስት ተከታታይ ዓመታት የኢንስቲትዩቱ የቴክኒካል አማካሪ ቦርድ አባላት በመሆን ያገለገሉ ባለሙያዎችን የሥራ ዘመን መጠናቀቅን በማስመልከት የተከናወኑ ሥራዎች አፈፃጸም እና የእውቅና መርሃ-ግብር አካሄዷል።
የማጠቃለያና የእውቅና መርሃ-ግብሩን በንግግር የከፈቱት የቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ነጋሽ እንደገለጹት፤ ተቋሙ በምስራቅ አፍሪካ የክህሎት ማሳደጊያና ቀጠናዊ ትስስር ፕሮጀክት (EASTRIP) ውስጥ አባል ተቋማት አንዱ ሆኖ ከተቀላቀለበት ጊዜ ጀምሮ በርካታ ስኬታማና ውጤታማ ሥራዎች መከናወናቸውን ገልጸው፤ ለዚህም ስኬት የቴክኒካል አማካሪ ቦርዱ የነበረው ሙያዊ ድጋፍ የጎላ ድርሻ እንደነበረው አስምረውበታል።
ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም ኢንስቲትዩቱ ወደ EASTRIP ፕሮጀክት የገባው ከሌሎች ተቋማት ዘግይቶ የነበረ ቢሆንም፣ በቦርዱና በሠራተኞች የተቀናጀ ጥረት በአጭር ጊዜ ውስጥ ስኬታማ ሥራ ማከናወን መቻሉን ገልጸዋል።
የቴክኒካል ቦርዱ ሰብሳቢ አቶ መልካሙ መኮንን በበኩላቸው በፕሮግራሙ ላይ ባደረጉት ንግግር ተቋሙ ይህንን ኃላፊነት ሰጥቶ በፕሮጀክቱ ጥቂት ሙያዊ አበርክቶ እንዲኖራቸው ዕድል ስላመቻቸላቸውና ላደረገላቸው እውቅና ለኢንስቲትዩቱ ያላቸውን ከፍ ያለ ምስጋና አቅርበዋል።
በዕለቱ በተካሄደው መርሃ-ግብር የፕሮጀክቱ አስተባባሪ አቶ አብርሃም ለገሰ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን፣ የተመዘገቡ ስኬቶችንና የተገኙ ውጤቶችን በዝርዝር የሚያሳይ የአፈፃጸም ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን በተነሱ ነጥቦች ላይም ውይይት ተደርጓል።
ይህ የእውቅና መርሃ-ግብር ተቋሙ ለባለሙያዎቹ ያለውን ክብር የገለጸበት መሰል ሀገራዊና ቀጠናዊ ፕሮጀክቶችን በላቀ ስኬት ለማስቀጠል ያለውን ዝግጁነት ያሳየበት ሆኖ ተጠናቋል።
ትክክለኛ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን ማስፈንጠሪያዎች ይጠቀሙ
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/tticommunication
ቴሌግራም ፡https://t.me/tticommunication
http://tiktok.com/
03/06/2026
ቲዎሪን በተግባር፡ የኢንስቲትዩቱ ሰልጣኞች በቢሾፍቱ የመስክ ምልከታ አካሄዱ
ቱ.ማ.ኢ
ግንቦት 26/2018 ዓ.ም
የፌደራል ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ሰልጣኞች በክፍል ውስጥ የተማሩትን የንድፈ-ሀሳብ ትምህርት ይበልጥ ለማጠናከር በቢሾፍቱ ከተማና አካባቢዋ በሚገኙ ውብ ሀይቆችና የቱሪስት መዳረሻዎች ላይ የተግባር ልምምድና የመስክ ምልከታ አካሄዱ።
ሰልጣኞቹ በጉብኝታቸው የቢሾፍቱን ታዋቂ ሀይቆች ስነ-ምህዳር እና የቱሪዝም እምቅ አቅም በተጨባጭ ተመልክተዋል፣ የዋና እና የጀልባ ጉዞ (Boating) ልምምድ አድርገዋል፡፡
የባቦጋያ እና ሆራ አርሰዲ ሀይቆች ታሪካዊ አመጣጥ ለአካባቢው ማህበረሰብ ስላላቸው ባህላዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ሰፊ ገለጻ በአስጎቢኚዎች ተደርጎላቸዋል።
በጉብኝታቸው በሆራ ሆራ አርሰዲ እና በቢሾፍቱ ሀይቆች ላይ የሚገኙ የተለያዩ ብርቅዬና ስደተኛ አእዋፋትን የተመለከቱ ሲሆን፣ ስለ አእዋፋቱ ዝርያዎች፣ ባህሪና ስለ ስነ-ምህዳር ጥበቃ ግንዛቤ አግኝተዋል።
በአጠቃላይ ለቱሪዝም ሰልጣኞች በሶስት ክፍል የተዘጋጀው የመስክ ምልከታና የተግባር ስልጠና አስመልክቶ የጉዞው አስተባባሪ እና የቱሪዝም ፋኩልቲ ዲን አቶ ሲሳይ አብርሃም እንደገለጹት ሰልጣኞቹ የወደፊት የቱሪዝም ባለሙያነታቸውንና የአስጎብኚነት ክህሎታቸውን ሊያሳድጉ የሚችሉ ተግባራዊ ልምዶችን የቀሰሙበት ነው ብለዋል፡፡
ይህን መሰል የተግባር ስልጠና የትምህርትን ጥራት ለማሻሻል እና በኢንዱስትሪው ውስጥ በቀጥታ መሰማራት የሚችሉ ብቁና ተወዳዳሪ ባለሙያዎችን ለማፍራት ትልቅ ሚና ይጫወታልም ብለዋል፡፡
ትክክለኛ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን ማስፈንጠሪያዎች ይጠቀሙ
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/tticommunication
ቴሌግራም ፡https://t.me/tticommunication
http://tiktok.com/
28/05/2026
የኢንስቲትዩቱ ሰልጣኞች በአንድነት ፓርክ እና በብሔራዊ ቤተመንግሥት፤
ቱ.ማ.ኢ
ግንቦት 20/2018 ዓ.ም
የፌዴራል ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት በየዓመቱ የቱሪዝም ትምህርት ክፍል ሰልጣኞች በንድፈሃሳብ የቀሰሙትን እውቀት በተግባር ለመደገፍ የሚያስችል ትምህርታዊ ጉብኝት ከሚወስዱባቸው መዳረሻዎች ለህዝብ ክፍት የተደረጉት አንድነት ፓርክና ብሔራዊ በተመንግስት ይጠቀሳሉ፡፡
እነዚህ መዳረሻዎች አዲስ አበባ ከተማ ከሚገኙ የታሪክ፣ የተፈጥሮና የባህል ቅርሶችን የያዙ በመሆናቸው ለሰልጣኞቻችን ጥሩ እድል ፈጥሯል ያሉት የጉብኝቱ አስተባባሪና የቱሪዝም ትምህርት ክፍል ኃላፊ አቶ ሲሳይ አብርሃም ናቸው፡፡
አቶ ሲሳይ ስለጉብኝቱ ዓላማ ሲገልጹ ሰልጣኞች ተግባራዊ እውቀት በመቅሰም የሀገራችንን ታሪካዊ፣ ባህላዊ እና ተፈጥሯዊ የቱሪስት መስህቦች አያያዝና አደረጃጀት በቅርብ እንዲረዱ ማስቻል፤ በፓርኮችና በቱሪስት መዳረሻ ሥፍራዎች የሚሰጡ አገልግሎቶችን በተግባር ማየትና ያሉ ከክፍተቶች በስልጠና መግደገፍ እንዲሁም የዘርፉን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ ነገ የኢትዮጵያን ቱሪዝም ለዓለም የሚያስተዋውቁ ብቁ ባለሙያዎችን ማፍራት ነው ብለዋል፡፡
በጉብኝቱ ወቅት ሰልጣኞቹ የሀገሪቱን አስደናቂ ታሪካዊ ቅርሶች፣ የተፈጥሮ ሃብቶች እና የቤተመንግሥቱን ልዩ የስነ-ህንጻ ጥበብ በጥልቀት የተመለከቱ ሲሆን ይህም ለቀጣይ ሙያዊ ጉዟቸው ትልቅ መነሳሳትን የፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል።
ትክክለኛ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን ማስፈንጠሪያዎች ይጠቀሙ
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/tticommunication
ቴሌግራም ፡https://t.me/tticommunication
http://tiktok.com/
26/05/2026
የፌዴራል ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ለእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለኢድ አል አድሃ (የአረፋ በዓል) በሰላም አደረሳችሁ እያለ መልካም ምኞቱን ይገልጻል፡፡
መልካም በዓል
26/05/2026
የኢንስቲትዩቱ ሰልጣኞች ትምህርታዊ ጉብኝት አደረጉ
ቱ.ማ.ኢ ግንቦት 18/2018 ዓ.ም
የፌዴራል ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት የቱሪዝም ትምህርት ክፍል ሰልጣኞች በአዲስ አበባ የሚገኙ የቱሪስት መዳረሻዎች ትምህርታዊ ጉብኝት አድርገዋል።
በዚህ ጉብኝት የአዲአበባ ዩንቨርሲቲ የእንስሳት ተፈጥሮ ቅርስ ጥበቃ መዘክር፣ የአድዋ ድል መታሰቢያ፣ የጉለሌ እጽዋት እና የእንጦጦ ፓርክ ተጎብኝቷል።
በጉብኝቱ የቱሪዝም ማኔጀመንት ሦስተኛ ዓመት፣ የቱርጋይድና የቱር ኦፕሬሽን አንደኛ እና ሁለተኛ ዓመት ሰልጣኞች በትምህርታዊ ጉብኝቱ እየተሳተፉ እንደሆኑ የቱሪዝም ፋካሊቲ ዲን አቶ ሲሳይ አብርሃም ተናግረዋል።
በዚህ ትምህርታዊ ጉብኝት የተሳተፉ ሰልጣኞች እንደተናገሩት ጉብኝቱ በንድፈ ያገኘነውን ዕውቀት በተግባር እንድናየው እድል የሰጠነው ብለዋል፡፡ ትምህርታዊ ጉብኝቱ በተለያዩ ቦታዎች የሚቀጥል ይሆናል።
ትክክለኛ መረጃዎችን ለማግኘት የሚከተሉትን ማስፈንጠሪያዎች ይጠቀሙ
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/tticommunication
ቴሌግራም፡https://t.me/tticommunication
http://tiktok.com/