25/05/2026
በእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ የ2017/18 ዓም ሻምፕዮን የሆነው አርሰናል ደጋፊዎች በአርባ ምንጭ ከተማ ጋሞ አደባባይ ከስጦታዎች ሁሉ የላቀ ስጦታ የሆነውን የደም ልገሳ መርሃ-ግብር በማከናወን ታሪካዊና አይረሴ ተግባር ፈጽመዋል።
የአርባ ምንጭ ደም እና ሕብረ -ህዋስ ባንክ አገልግሎት በርሃ-ግብሩ ለተሳተፉ በጎ ፈቃደኛ ደም ለጋሾች እንዲሁም አስተባባሪዎች በሙሉ ከፍ ያለ ምስጋናዉን ያቀርባል።
ግንቦት 16/2018 ዓም
አርባ ምንጭ፤
24/05/2026
በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የአርሴናል ደጋፊዎች የደም ልገሳ መርሃ-ግብር በአርባ ምንጭ ጋሞ አደባባይ በይፋ ተጀምሯል
22/05/2026
የአርባ ምንጭ ደም እና ሕብረ - ህዋስ ባንክ አገልግሎት ከብርብር የመጀመሪያ ጀረጃ ሆስፒታልና እና ከምዕራብ አባያ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ጋር በመተባበር ለትምህርት ቤቱ ተማሪዎችና መምህራን ስለበጎ ፈቃድ ደም ልገሳ ቅስቀሳና የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት በመስጠት የደም ልገሳ መርሃ - ግብር አከናወነ።
በመረሃ - ግብሩ ፈቃደኛ የሆኑ በጎ ፈቃደኛ የትምህርት ቤቱ ተማሪዎችና መምህራን እንዲሁም የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታሉ ሠራተኞች ተሳትፈዋል።
የአርባ ምንጭ ደም እና ሕብረ -ህዋስ ባንክ አገልግሎት ሆስፒታሉ እና ት/ቤቱ በመቀናጀት ላደረጉት ትብብር እንዲሁም በደም ልገሳ መርሃ ግብሩ ለተሳተፉ በጎ ፈቃደኛ ደም ለጋሾች በሙሉ ከፍ ያለ ምስጋናዉን ያቀርባል።
ግንቦት 14/2018 ዓም
አርባ ምንጭ፤
20/05/2026
ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ሊያውቀዉና ሊገነዘብ የሚገባው ወሳኝ መረጃ!
20/05/2026
በሚተካ ደም መተኪያ የሌለውን ክቡሩን የሰው ህይወት ይታደጉ!
18/05/2026
የአርባ ምንጭ ደም እና ሕብረ -ህዋስ ባንክ አገልግሎት ከማህበረ ቅዱሳን አርባ ምንጭ ማዕከል ጋር በመተባር ለሁለት ተከታታይ ቀናት የደም ልገሳ መርሃ ግብር አከናወነ።
መርሃ -ግብሩ ከቀን 08-09/9/2018 ዓም የተከናወነ ሲሆን በሂደቱ ከተለያዩ አጥቢያ የተወጣጡ ማህበረ ምዕመናን ተሳትፈዋል።በዚህም ከመቶ አርባ አምስት (145) ዩኒት በላይ ደም ለመሰብሰብ ተችሏል።
የአርባ ምንጭ ደም እና ሕብረ -ህዋስ ባንክ አገልግሎት ቤተክርስቲያኒቱና ማህበሩ በመቀናጀት ላደረጉልን ትብብር እንዲሁም በደም ልገሳ መርሃ ግብሩ ለተሳተፉ ማህበረ ምዕመናን በሙሉ እጅግ በጣም ከፍ ያለ ምስጋናዉን ያቀርባል።
ግንቦት 10/2018 ዓም
አርባ ምንጭ
17/05/2026
በአርባምንጭ ከተማ አስተዳደር በሲቀላ ክፍለ ከተማ "ደሜን ለወገኔ ካርዴን ለብልጽግና" በሚል መሪ ቃል የደም ልገሳ መርሃ-ግብር ተካሂደ።
በመርሃ-ግብሩ የአርባ ምንጭ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ የፖለቲካና ህዝብ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሐብታሙን ጨምሮ የክፍለ ከተማው እና የቀበሌ አመራሮች እንዲሁም በርካታ ወጣቶች ተሳትፈዋል።
ግንቦት 0972018
አርባ ምንጭ