31/05/2026
የጥሞና ጊዜ የመጨረሻ ቀን ምሽት ላይ ሆነን የሙሽሪት አርባምንጭን የኮርደር ልማት በእግራችን ተዘዋውረን ሲንጎበኝ
ግርምት የፈጠረብን የከተማችን ነዋሪዎች እንዲሁም ቱርስቶች በዋናው መንገድ ግራና ቀኝ ሲዝናኑ ስናይ እጅግ ደስ ብሎናል።
በመጨረሻም በዞናችን ፓርቲ ጽ/ቤት ግቢ በተዘጋጀው የቡና ቅጠል፣ ኤንገሬ ቦዬ ስኳር ድንች በዳጣ እራት ተጋበዝን።
የኢፌዲሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፌ ጉባኤ ክቡር አቶ ታገሰ ጫፎ፣ የክልላችን ፕረዝዳንት ክቡር አቶ ጥላሁን ከበደና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮቻችን ተገኝተዋል።
29/05/2026
በጥሞና ጊዜ ጀልባችንን ይዘን ወደነጭ ሳር ብሔራዊ ፓርክ የሜዳ አህያና ውብ ተፈጥሮ ለማድነቅ ፈቀቅ ብለናል።
የጋሞ ልማት ማህበራችን ሁሌም ቀዳሚ!
Visit Gamo!
27/05/2026
በአርባ ምንጭ ዙሪያ ደጋ ሻራ ቀበሌ
ከጊላ ተራራ ስር እዶ ገበያ ላይ ሆነን የአያታችን መንደር ሚሎን ጎበኘን። ያኔ ድሮ የነበረውን የማህረሰቡን ፍቅርና ህብረት አስታወሰኝ።
መልካም ምሽት!
27/05/2026
ሌላኛው የህዝብ ማዕበል በጨንቻ ምርጫ ክልል
እኛ ካለን መረዳት በላይ ህዝባችን ለፓርቲያችን ያለውን አጋርነት በተግባር በሰልፍም አረጋገጡልን። እናመሠግናለን!!!
የአፕል የወተት የእንሰት የድንችና የሽመና ጥበብ ምድር ጨንቻ !!
የስንዴ ነዶ እንምረጥ!!
27/05/2026
ጋሞ ዞንን የወተት ሐይቅ የቅቤ ተራራ የማድረግ ራዕይ አንግቦ የተነሳው ያላ የወተት ማቀነባበሪያ ፋብሪካ ተመረቀ።
ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በአርባ ምንጭ ከተማ ከ75 ሚሊዮን ብር በላይ ካፒታል የተገነባ "ያላ የወተት ማቀነባበሪያ" ፋብሪካን መርቀው ከፍተዋል።
ያላ የወተት ማቀነባበሪያ" ፋብሪካ በቀን 24 ሺህ ሊትር ጥራት ያለው ወተት የሚያቀነባብር ከመሆኑም በላይ ለ150 ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የስራ ዕድል መፍጠሩንና ከ5 ሺህ በላይ የሚሆኑ አርሶ አደሮች በእሴት ሰንሰለት ተጠቃሚ የሚያደርግ መሆኑን ተገልጿል።
ፋብሪካው ፓስቸራይዝድ ወተት፣ ተፈጥሮዓዊ እርጎ፣ የፈረንጅ አይብ፣ ክሬምና ባህላዊ አይብ እንደሚያመርትም ተገልጿል።
26/05/2026
መገረምና መደነቅ በህዝብ ማዕበል!!
የፓርቲያችን ብልጽግና ዞናዊ የምርጫ ቅስቀሳ ማጠቃለያ የህዝብ ማዕበል ከሁሉም መዋቅራችን የብልጽግና ቤተሰብ አባላት በዞናችን መዲና በሙሽሪት አርባምንጭ ከተማ ለተገኛችሁ ታላቅ ምሥጋና አቀርባለሁኝ።
የስንዴ ነዶ የምርጫ ምልክታችንን እንምረጥ!!
25/05/2026
ህዝቡ ብልጽግና በተግባር ተፈትኖ ውጤታማ ፓርቲ መሆኑን በድጋፉ አሳይቶናል። እናመሠግናለን!!
የቁጫ ምርጫ ክልል ማጠቃለያ
25/05/2026
ብርብር በለውጥ ጎዳና
የብርብር ከተማ አስተዳደር የማዘጋጃቤታዊ አገልግሎት በማዘመን ከክልሉ ፈርጅ 3 ከተሞች ቀዳሚ ሆነ።
ቀጥለንም በአጭር ጊዜ ተገንብቶ ለአገልግሎት የበቃውን የገቢና ፋይናንስ ጽ/ቤት ህንጻ አስመርቀን የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ህንጻ ስራ አስጀምረናል።