22/05/2026
Aysaqiti Daqarak Qafiyat K/buxa Aysaita Woreda Health Office
only community service
22/05/2026
22/05/2026
16/05/2026
16/05/2026
14/05/2026
ከ69 ሚሊየን በላይ ዜጎች የጤና መድህን አገልግሎት ተጠቃሚ ሆነዋል
++++++++++++++
| በመላ ሀገሪቱ ከ69 ሚሊየን በላይ ዜጎች የጤና መድህን አገልግሎት ተጠቃሚ መሆናቸውን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 20ኛ መደበኛ ስብስባ የጤና ሚኒስቴርን የእቅድ አፈጻጸም በገመገመበት ወቅት የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ እንደተናገሩት፣ የጤና መድህን ሥርዓት በርካታ ዜጎችን ያቀፈና የአገልግሎቱ ፈላጊዎች ቁጥርም ዕድገት የታየበት ነው። ለዚህም የግብዓት ዕጥረት እንዳይፈጥር በትኩረት እየተሰራ ይገኛል ብለዋል።
ከሚያስፈልገው የመድኃኒት አቅርቦት 70 በመቶ የሚሆነውን በኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት በኩል ለማሟላት እየተሠራ ሲሆን ቀሪው በመንግሥትና በግል አጋርነት የሚሸፈን ይሆናል ብለዋል።
በ"ኢትዮጵያ ታምርት" ንቅናቄና ለሀገር ውስጥ አምራቾች በተሰጠው ድጋፍ፣ የሀገር ውስጥ የመድኃኒት አቅርቦት ድርሻም 46 በመቶ መድረሱ አመላክተዋል።
ጠንካራ የጤና ፋይናንስ ሥርዓት በመዘርጋትና አሠራሮችን በማዘመን ለዜጎች የተቀላጠፈ አገልግሎት ለመስጠት በትኩረት እየተሠራ እንደሚገኝም ሚኒስትሯ ጠቁመዋል።
የጤና ሚኒስትር ዶክተር መቅደስ ዳባ ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባለት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ማብራሪያ በመላው ሀገሪቱ 69 ሚሊየን ዜጎች የጤና መድህን አገልግሎት ተጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በክብረአብ በላቸው
#ጤናመድህን #የተቋማትግንባታ #ሆስፒታል
Cliquez ici pour réclamer votre Listage Commercial.
Emplacement
Contacter l'entreprise
Site Web
Adresse
Democratic Republic Of The
