09/06/2026
We Reaffirm our Commitment to Global Cooperation
-------------------------------------------------------
The Financial Intelligence Service of Ethiopia proudly celebrates International FIU Day! We reaffirm our commitment to global cooperation and the fight against money laundering and terrorist financing. Together, we make financial systems safer.
On International FIU Day, Financial Intelligence Service of Ethiopia reflects on our mission: protecting financial integrity and combating financial crime. We stand united with FIUs worldwide to deliver results that matter.
Financial Intelligence Service of Ethiopia joins the global FIU community in celebrating International FIU Day! This year in the last nine months alone, we are proud of providing 153 spontaneous financial intelligence outputs to the LEAs and 375 upon request supports to local stakeholders and international partners. Together, we strengthen the AML/CFT framework.
Financial Intelligence Service of Ethiopia celebrates International FIU Day and looks forward to advancing innovation, cooperation, and resilience in the fight against financial crime.
Today is International FIU Day! Financial Intelligence Service of Ethiopia invites partners and stakeholders to continue working together to detect, disrupt, and prevent financial crime. Collaboration is key.
# EthiopianFIU
09/06/2026
Celebrating International FIUs Day !
Celebrating International FIU Day - June 9
📢 🌐 International FIU Day launches on 9 June.🛡️ This inaugural an...
28/05/2026
የመንግስት እና የግሉ ዘርፍ
-------------------
ግንቦት 20 ቀን 2018 ዓ.ም
በወንጀል ድርጊት የተገኘ ገንዘብ ወይም ንብረት ህጋዊ አስመስሎ ማቅረብ፣ ሽብርተኝነትንና ጅምላ ጨራሽ መሣሪዎች ብዜትን በገንዘብ መደገፍ ወንጀሎች መከላከልና መቆጣጠር ቅንጅታዊ ሥራዎች ማጠናከር ዙሪያ ከመንግስትና የግሉ ዘርፍ ከተውጣጡ የሚመለከታቸው አመራሮችና ባለሙያዎች ጋር ስልጠናና ውይይት እየተካሄደ ነው።
26/05/2026
እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል አድሐ በዓል አደረሳችሁ !
26/05/2026
55ኛ መደበኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ውሳኔዎች
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ግንቦት 18 ቀን 2018 ዓ.ም ባካሄደው 55ኛ መደበኛ ስብሰባ በህግ የሰውነት መብት የተሰጣቸው አካላት ተጠቃሚ የሚሆኑ ባለቤቶችን መረጃ ግልጸኝነት ለመደንገግ የቀረበ ረቂቅ ደንብ ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል፡፡ በወንጀል ድርጊት የተገኘ ገንዘብ ወይም ንብረት ሕጋዊ አስመስሎ ማቅረብንና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣውን አዋጅ በአግባቡ ለማስፈጸም እንዲያስችል ረቂቅ ደንቡ ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በቀረበው ረቂቅ ደንብ ላይ በሰፊው ከተወያየበት በኋላ ግብአቶችን በማከል ደንቡ በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ተግባራዊ እንዲደረግ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡
25/05/2026
PUBLIC NOTICE FROM NATIONAL BANK OF ETHIOPIA
------------------------------------------------------------------------
PUBLIC NOTICE
NOTICE ON FX DIRECTIVE AMENDMENT AND RATIONALIZATION OF FEES AND CHARGES ON LETTERS OF CREDIT
25 May 2026 | Addis Ababa, Ethiopia
The National Bank of Ethiopia, as part of its ongoing transition toward a market-based foreign exchange regime, has been implementing a series of carefully sequenced reforms to strengthen the efficiency, transparency, and competitiveness of the foreign exchange market.
Since the introduction of the market-based foreign exchange regime in July 2024, the NBE has continued to advance reforms aimed at establishing a well-functioning foreign exchange system that aligns with international best practices. These efforts have contributed to notable progress in enhancing market operations and supporting foreign exchange market stability.
Despite these improvements, further amendment to the FX Directive has become necessary to relax foreign exchange administration and approval bottlenecks for ease of doing business and thereby strengthen the development of foreign exchange market. In this regard, the articles of FXD/01/2024 are hereby amended as follows:
I. Amendment to FX Directive No. FXD/01/2024
1. Banks are authorized to approve Letters of Credit on acceptance for institutions holding foreign currency accounts, and retention accounts holders, without prior approval of NBE.
2. Banks are authorized to approve Cash Against Documents on acceptance for institutions holding foreign currency accounts, and retention account holders, without prior approval of NBE.
3. Institutions holding foreign currency accounts, including retention account holders, may order or initiate shipment of goods under Cash Against Documents arrangements without prior approval of Banks. Payment processing shall be subject to the submission and verification of the required documents.
II. Rationalization of Fees and Charges on Letters of Credit
The structure of fees and charges applied by commercial banks on foreign exchange related Letter of Credit (LC) transactions remain inconsistent with prevailing global norms. In view of this, the NBE has undertaken a rationalization of fees and charges on LC arrangements to ensure alignment to international standards.
Accordingly, the National Bank of Ethiopia hereby instructs all banks to implement the following:
1. Fees and charges applicable to Letter of Credit transactions for institutions holding foreign currency accounts, including retention account holders, shall be determined on an annualized basis and applied pro-rata in accordance with the tenor of the respective Letter of Credit.
2. The annualized fee rate applicable to Letter of Credit transactions shall not exceed the maximum limit previously set by the National Bank of Ethiopia.
This measure is intended to ensure that LC-related charges are competitive and consistent with international pricing practices. It is also expected to reduce transaction costs for importers and exporters, enhance the competitiveness of Ethiopia’s trade finance environment, and further strengthen the credibility and effectiveness of ongoing foreign exchange reforms.
The National Bank of Ethiopia will continue to monitor developments closely and take additional measures as necessary to support a stable and efficient foreign exchange market.
22/05/2026
በፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት በስነ-ምግባር ደንብ፣ በጥቅም ግጭት ምንነት፣ መንስኤዎችና መከላከያ እርምጃዎች ላይ ለሰራተኞች ስልጠና ተሰጠ።
21/05/2026
በንግድ ሽፋን የወንጀል ገንዘብ ማፅዳት እንዴት ይፈፀማል?
-----------------------------------------------------
ወንጀለኞች የንግድ ግብይቶችን በማጭበርበር ገንዘብ ከአንድ አገር ወደ ሌላ አገር ያሸጋግራሉ። እንዴት?
• ለንግድ እቃዎች ዋጋ ከእውነተኛው የገበያ ዋጋ በላይ ደረሰኝ በማቅረብ (Over-Invoicing) ተጨማሪ ክፍያ እንዲፈጸም ማድረግ፣
• ለንግድ እቃዎች ዋጋ ከእውነተኛው የገበያ ዋጋ በታች የሆነ ደረሰኝ በማቅረብ (Under-Invoicing) ዋጋን ወደ ውጭ ሀገር ማሸጋገር፣
• የእቃዎችን መጠን፣ ጥራት ወይም ዓይነት በሐሰት ማቅረብ፣
• የተላኩ የንግድ ዕቃዎች ከቀረቡ ሰነዶች ጋር የማይጣጣሙ መሆን፣
• የንግድ ዕቃዎችን ግንኙነት ባላቸው ወይም እህት ድርጅቶች መካከል በተደጋጋሚ እንዲላላክ በማድረግ የንግድ እንቅስቃሴ ያለ ለማስመሰል ሀሰተኛ የንግድ እንቅስቃሴ መፍጠር፣
• የንግድ ሰነዶችን ሙሉ በሙሉ በሐሰት ማዘጋጀት
ከሚጠቀሙባቸው ዘዴዎች መካከል ናቸው።
20/05/2026
የአካውንት እና የግብይት እንቅስቃሴ የስጋት/አደጋ ምልክቶች
--------------------------------------------------------------
በንግድ ላይ የተመሰረተ ከወንጀል ተግባር የተገኘ ገንዘብ እንዳይታወቅ የማድረግና የማፅዳት የወንጀል ተግባራት አመላካች የስጋት ምልክቶችን ከንግዱ መዋቅራዊ ሁኔታ፣ ከንግድ ድርጅት የንግድ ተግባራት፣ እንዲሁም ከንግድ ሰነዶችና ዕቃዎች አንፃር አስቀድመን ተመልክተናል።
በዚህ ፅሑፍ ከአካውንት እና የግብይት እንቅስቃሴ ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ የወንጀል ስጋት/አደጋ ጠቋሚ ምልክቶች እነዚህ ናቸው፦
1. የክፍያ ሁኔታ በመጨረሻ ሰዓት መቀየር
የንግድ ድርጅት ክፍያውን በመጨረሻ ሰዓት ወደ ያልታወቀ አካል መለወጥ ወይም የክፍያ ቀን/መጠን ለመቀየር መጠየቅ።
2. ከንግድ ተፈጥሯዊነት ውጭ የሆነ ከፍተኛ ግብይት
አካውንቱ ከተገለጸው የንግድ እንቅስቃሴ ጋር የማይጣጣሙ በቁጥር ወይም በዋጋ ከፍተኛ ግብይቶችን ማሳየት።
3. “መሻገሪያ/Pay-through” አካውንት መጠቀም
ከፍተኛ ግብይት በፍጥነት መካሄድ እና በቀኑ መጨረሻ ትንሽ ቀሪ ገንዘብ ብቻ መኖር።
ከውጭ ለሚመጡ የንግድ እቃዎች የሚከፈለው ክፍያ ከእቃዎቹ ተቀባይ ውጭ ባለ አካል ይፈጸማል። ይህም ግልጽ የኢኮኖሚ ምክንያት የሌለው ሲሆን ለምሳሌ በንግድ ግብይቱ ውስጥ ያልተሳተፈ በተሸፈነ (በተደበቀ) ኩባንያ ወይም በፊትለፊት ኩባንያ ሊፈፅም ይችላል።
4. ክፍያ በሶስተኛ ወገን መፈፀም
ከእቃ ተቀባይ ውጭ ያለ አካል (shell/front Company) ክፍያ መፈፀም።
5. የግብይት ሪፖርቶች ተደጋጋሚ ከገደብ በታች መሆን፣
ግብይቶች ሁልጊዜ ከሪፖርት ገደብ በታች መኖር። የንግድ ድርጅቱ የጥሬ ገንዘብ ተቀማጭ ወይም ሌሎች ግብይቶች በተደጋጋሚ ከሚጠየቀው የሪፖርት ገደብ በታች ብቻ ሆነው ይታያል።
6. ድንገተኛ የግብይት እድገት እና በድንጋት መዝጋት
ከንግድ ድርጅቱ ጋር የተያያዙ የግብይት እንቅስቃሴዎች በፍጥነት እና በከፍተኛ መጠን ይጨምራሉ። ከዚያም ከአጭር ጊዜ በኋላ ድንገት እንቅስቃሴ ይቆማል።
7. በዙር መጠን ክፍያዎችን መፈፀም
በዘርፉ ያልተለመዱ ከፍተኛ መጠን ያለው ክፍያ በዙር ይፈፀማሉ።
8. የፈንድ ምልልስ
ገንዘብ ከአንድ አገር ወደ ሌላ አገር ወጥቶ እና በሌሎች አገራት ካለፈ በኋላ ወደ መጀመሪያው አገር ይመለሳል።
15/05/2026
ከንግድ ሰነዶች እና ሸቀጦች ጋር የተያያዘ የወንጀል ገንዘብ ህጋዊ ማስመሰል ስጋት ማሳያዎች
------------------------
በንግድ ሽፋን የወንጀል ገንዘብ ህጋዊ የማስመሰል የወንጀል ተግባር ከሚፈፀምባቸው መንገዶች መካከል የንግድ ሰነዶችን እና የሸቀጦችን መግለጫዎች በመጠቀም ነው። ከዚህ የወንጀል ተግባር ጋር በተያያዘ የተለመዱ ስምንት የስጋት ማሳያ ምልክቶች የሚከተሉት ናቸው።
1. በኮንትራት ውሎች፣ በደረሰኞች ወይም ሌሎች የንግድ ሰነዶች ላይ የወጥነት ማጣት ሁኔታ መኖር፦ በወጪ ንግድ ላኪ ድርጅት ስም አካል እና በክፍያ ተቀባይ ድርጅት ስም መካከል አለመጣጠም መኖር፣ በዋጋ ደረሰኞች እና የውል ስምምነቶች መለያየት ወይም በእቃዎቹ ብዛት፣ ጥራት፣ መጠን ወይም ዋጋ እና መግለጫዎቻቸው ጋር በተያያዘ ልዩነቶች መኖር እንደ ማሳያ ይጠቅማል፤
2. ኮንትራቶች፣ ደረሰኞች ወይም ሌሎች የንግድ ሰነዶች ከንግድ ነክ ጉዳዮች ጋር የማይጣጣሙ፣ ከገበያ ዋጋ ጋር የማይጣጣሙ ወይም ከቀደሙት ተነፃፃሪ ግብይቶች አኳያ በእጅጉ ተለዋዋጭ የሆኑ ክፍያዎችን ወይም ዋጋዎችን የያዙ ከሆኑ፤
3. የእቃዎቹ መግለጫ ግልጽ አለመሆን፦ የንግድ ሰነዶች (ኮንትራት፣ ኢንቮይስ ወይም ሌሎች የንግድ ሰነዶች) ስለሚነገዱት እቃዎች በጣም ጥቅል ወይም ግልጽ ያልሆነ መግለጫ ብቻ የያዙ ሆነው መገኘት።
4. ችግር ያለባቸው የንግድ ሰነዶች፦ ግብይቱን የሚደግፉ የንግድ ወይም የጉምሩክ ሰነዶች አለመኖር፣ ሀሰተኛ የሚመስሉ፣ ሐሰተኛ ወይም አሳሳች መረጃ የያዙ፣ ቀደም ሲል ውድቅ የተደረጉ ሰነዶችን ዳግም አያይዞ የማቅረብ፣ በሰነዶቹ ላይ ተደጋጋሚ ማሻሻያ ወይም ማስተካከያ የሚደረግባቸው ከሆነ፤
5. የኮንትራቶች በጣም ቀላል ሆኖ መገኘት፦ ከውስብስብ ወይም መደበኛ የንግድ ግብይቶች ጋር ተያይዘው የሚቀርቡ ኮንትራቶች በጣም ቀላል እና ያልተለመደ አደረጃጀት ያላቸው ከሆኑ በንግድ ሽፋን የወንጀል ገንዘብ ህጋዊ የማስመሰል ስጋት አንዱ ምልክት ሊሆን ይችላል። ለምሳሌ በኦንላይን/በኢንተርኔት ላይ በቀላሉ የሚገኙ ናሙና የኮንትራት አደረጃጀቶችን ተከትሎ የተዘጋጀ ሊሆን ይችላል።
6. የአስመጭና የወጪ ንግድ ዋጋ ከባንክ ማስተላለፊያዎች ጋር ትልቅ ልዩነት ማሳየት፦ የአንድ ድርጅት የተመዘገቡ የአስመጭ እቃዎች ዋጋ ከውጭ ባንኮች ለአስመጭ ከሚደረጉ የገንዘብ ማስተላለፍ መጠን ጋር ከፍተኛ ልዩነት ያለው ሆኖ ሊገኝ ይችላል። በሌላ በኩል ደግሞ የተመዘገቡ የወጪ እቃዎች ዋጋ ከገቢ የውጭ ባንክ የገንዘብ ማስተላለፍ መጠን ጋር ያለው ልዩነት ሰፊ ሆኖ ሲገኝ።
7. ጊዜያዊ አስመጭ ስርዓት ወደ አገር ውስጥ የገቡ እቃዎች በሀሰተኛ ሰነዶች ተደግፈው ተመልሰው ወደ ውጭአገር የመላክ ሁኔታ ሲኖር፤
8. ምንም አይነት የንግድ ወይም ኢኮኖሚያዊ ምክንያት ሳይኖር እቃዎች በብዙ ሀገራች ውስጥ እንዲያልፉና እንዲጓጓዙ የማድረግ ሁኔታ ሲኖር በወንጀል ተግባር የተገኘ ገንዘብ ህጋዊ ለማስመሰልና በመደበኛ የንግድ ስርዓት ውስጥ ለማስገባት የሚደረግ ሂደት መኖሩን የምጠቁም ቀይ መብራት በመሆኑ ተገቢውን የመከላከልና የመቆጣጠር እርምጃ መውሰድ ይጠይቃል።